የአሰቦት ደብረ ወገግ
ቅድስት ሥላሴና አባ ሳሙኤል ገዳም ደን የካቲት 20 ቀን 2004 ዓ.ም. ባልታወቀ ምክንያት በተነሣ እሳት ቃጠሎ ደረሰበት፡፡
ትላንት ከቀኑ 5፡00 ሰዓት የተነሣው እሳት እስከ አሁን ድረስ ያልጠፋ መሆኑንን የገለጹት የገዳሙ አገልጋይ አባ ወልዴ እንዳሉት እሳቱ እየተስፋፋ ከደኑ አልፎ ወደ ቅድስት ሥላሴ የአባቶች ገዳም እየተቃረበ መሆኑንን ገልጸዋል፡፡
እሳቱን ለማጥፋት የአካባቢው ገበሬ ማኅበር ጥረት እያደረገ ቢሆንም ከውኃ እጥረትና ከሰው ኀይል ማነስ
የተነሣ ይህ ዜና እስከ ተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ እሳቱ አለመጥፋቱን ለማወቅ ተችሏል በማለት የማህበረ ቅዱሳን ድረገፅ ገልፃል፡፡
No comments:
Post a Comment
ማህበረ ቅዱስ አሞኒ