Wednesday, August 22, 2012

የብፁዕ ወቅዱስ ዶ/ር አቡነ ጳውሎስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት የዓለም ሃይማኖቶች ለሰላም የክብር ፕሬዝዳንት የዓለም የሰላም አምባሳደር የቀብር ሥነ ሥርዓት የወጣ መርሐ ግብር

"ለፈራሔ እግዚአብሔር ይሤኒ ደኅሪቱ፣ ወይትባረክ ዕለተ ሞቱ"
"እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው ፍፃሜው ያምራል፡፡ በሚሞትበትም ቀን ይከበራል" ሲራ. 113፡፡
     የብፁዕ ወቅዱስ / አቡነ ጳውሎስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ፕሬዝዳንት የዓለም ሃይማኖቶች ለሰላም የክብር ፕሬዝዳንት የዓለም የሰላም አምባሳደር የቀብር ሥነ ሥርዓት የወጣ መርሐ ግብር

/           
       
          ሰዓት

                                                    ክንውን
1
ጠዋት 1200 
 ረቡዕ ነሐሴ 16 ቀን 2004 . በኢትዮጵያ ገዳማትና አድባራት 10 ደቂቃ ያህል የደወል ድምጽ ይሰማል፡፡                   
2
ከቀኑ 500 - 530
በዚሁ ዕለት ከቀኑ 500 ሰዓት የቅዱስነታቸው አስከሬን በብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት፣
የጠቅላይ ቤተ ክህነት የየመምሪያው ኃላፊዎችና መላው ሠራተኞች፣ የየድርጅቱና የየኮሌጁ ኃላፊዎችና ሠራተኞች፣ 
የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራ አስተዳዳሪዎች፣ ጸሐፊዎች፣ ሠራተኞች፣ መላ አገልጋዮች በክብር ታጅቦ ከመንበረ ፓትርያርክ 
ወደ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም ቤተ ክርስቲያን ይገባል፡፡
3
ከቀኑ 530 – 830
 የቅዳሴ ሥነ ሥርዓት ይከናወናል፡፡
4
ከቀኑ 830 – 1200

የቅዳሴው ሥነ ሥርዓት እንዳበቃ አስከሬኑ ከመንበረ ፓትርያርክ ቅድስተ ቅዱሳን ማርያም ገዳም በልዩ ሰረገላ ሆኖ
በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣ በክቡራን ምኒስቴሮችና የመንግሥት ባለ ሥልጣናት፣ በገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣
 በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት /ቤት ወጣቶች፣ በፖሊስ ሠራዊት ባንድ፣ በምዕመናንና ምዕመናት በክብር ታጅቦ
ወደ መንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጉዞ ያደርጋል፡፡ በዚህ ጉዞ ላይ የፖሊስ ሠራዊት ግራና ቀኝ በሰልፍ አስከሬኑን ያጅባል፡፡
የቅዱስነታቸው አስከሬን በመንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እንዳረፈ የዕለቱ መርሐ ግብር በጸሎት ይዘጋል፡፡
5
ከምሽቱ 200 -
ንጋቱ 1200
ረቡዕ ለሐሙስ /16 17/ አጥቢያ  ከምሽቱ 200 ሰዓት እስከ ንጋቱ 12 ሰዓት ሌሊት ሙሉ ጸሎተ ማኅሌቱ ሲከናወን ያድራል፡፡
6
ሐሙስ ጠዋት
1200 – 230
ሐሙስ ከንጋቱ 1200 ሰዓት አስከሬኑ ባረፈበት በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ጸሎተ ቅዳሴ በብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት አኀት አብያተ
ክርስቲያናት ተወካዮች ባሉበት ይከናወናል
7
ሐሙስ ጠዋት
230 – 300
ጸሎተ ቅዳሴው እንዳበቃ የቅዱስነታቸው አስከሬን በክብር ታጅቦ ወደ አውደ ምሕረቱ ወጥቶ በተዘጋጀለት ቦታ ያርፋል፡፡
8
ሐሙስ ጠዋት
240 – 310
በአውደ ምሕረቱ ላይ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት፣ ከፍተኛ የመንግሥት ባለ ሥልጣናት፣ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር እንግዶች በተዘጋጀላቸው
የክብር ቦታ ይቀመጣሉ፡፡
9
310 – 320
የዐውደ ምሕረቱ ፕሮግራም በጸሎት እንደተከፈተ ጸሎተ ወንጌሉ ይደርሳል፡፡
10
320 – 335
ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ያሬዳዊ ወረብ ያቀርባሉ፡፡
11
335 – 345
የሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች መዝሙር ያቀርባሉ፡፡
12
345 – 400
ሦስት ሊቃውንት ቅኔ ያቀርባሉ፡፡
13
400 – 420
የቅዱስነታቸው የሕይወት ታሪክ በቅዱስ ሲኖዶስ ተወካይ ይቀርባል፡፡
14
420 – 430
የተከበሩ የኢፌዲሪ ፕሬዝዳንት ንግግር፣
15
430 – 440
የተከበሩ የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚኒስቴር ተወካይ ንግግር፣
16
440 – 500
የአኃት አብያተ ክርስቲያናት ፓትርያርኮች፣ አባቶችና ተወካዮች ንግግር፣
17
500 – 505
የምሥራቅ አብያተ ክርስቲያናት ተወካይ ንግግር፣
18
505 – 510
የሮም ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ፖፕ ተወካይ የፖንቲፊካል ካውንስል ፕሬዝዳንት ካርዲናል ንግግር፣
19
510 – 515
የኖርዌ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ንግግር
20
515 – 520
የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ዋና ጸሐፊ ንግግር፣
21
520 – 525
የዓለም ሃይማኖቶች ምክር ቤት ለሠላም ተወካይ ንግግር
22
525 – 530
የሁሉም የአፍሪካ አብያተ ክርስቲያናት ምክር ቤት ዋና ጸሐፊ ንግግር፣
23
530 – 535
የኢትዮጵያ የሃይማኖት ተቋማት የጋራ ጉባኤ ተወካይ ንግግር፣
24
535 – 540
የቅዱስነታቸው ቤተሰብ ተወካይ ንግግር፣
25
540 – 600
የቅዱስ ሲኖዶስ ተወካይ ንግግር ያደርጋሉ
26
600 – 615
አስከሬኑ በተዘጋጀለት ቦታ በክብር እንዳረፈ፤ የቀብሩ ሥነ ሥርዓት ጸሎትና ቃለ ምዕዳን ተሰጥቶ ስንብት ይደረጋል፡፡

No comments:

Post a Comment

ማህበረ ቅዱስ አሞኒ