/በደረጀ ነጋሽ ዘወይንዬ/
ዓርብ የካቲት 16/2004 ዓ.ም በጠዋቱኑ እጅግ በርካታ ምዕመናን በቅርብ በተገኘው የለገዳዲ ኬማ ዋሻ ፍልፍል ቤተክርስቲያን በአግራሞትና አድናቆት ተሰብስበዋል፡፡ በአካባቢው ድንኳኖች ተጥለዋል፡፡ አንዳንዶች ዋሻ ሲጎበኙ ሌሎች ደግሞ ፀበል ይጠመቃሉ፡፡ አንዳንዶች ይፀልያሉ ሌሎች ደግሞ ይነጋገራሉ፡፡ የከተማው ወይዛዝርት ለመስተንግዶው ይፋጠናሉ፡፡ እሺ ብላ ከዋሻው ትወጣ ይሆን? ወደ ዋሻው ካልተመለሰችስ? ብቻ የየራሳቸውን አስተያየት ይሰጣሉ፡፡ ለገዳዲ ከተማ ከአዲስ አበባ 25ኪ.ሜ ርቀት ላይ በኮተቤ መስመር ለገጣፎን አልፈው የምትገኝ ከተማ ስትሆን በወታደር ማሰልጠን፣ በትምህርት ስርጭት እና በውሃ አቅርቦት ትታወቃለች፡፡ ለገዳዲ ማለት በኦሮምኛ የጠጅ ወንዝ ማለት ነው፡፡ በዚህ ቦታ ገበሬዎች የፈረሰ ቤተክርስቲያን፤ ፀበል ይገኛል፣የአባቶቻችን መካነ መቃብር እዚህ ነው እያሉ በጉልበት ያለፍቃዳቸው አስፈራርተዋቸው ቦታውን ለኤንጂኦ ተሰጠ፤ አራት ዓመት ምንም ሳይሰራበት ቆየ፡፡ በብዙ ተንኮል ያገኘውን የቤተክርስቲያን የሃይማኖት ቦታ ሊሠራበት አጥር ማጠር ሲጀመር ዋሻ እንዳለ ለአባቶቻችን በህልም ታያቸው፡፡ ወደ ቦታው ሲሄዱ ከስር ከወንዝ አደገኛ ገደል ላይ ትንሽ ቀዳዳ ዐዩ፡፡ አፈር ሲቆፍሩ ፍልፍል ዋሻውን አገኙ፤ ዋሻው በሶስት ይከፈላል፡፡ የመጀመሪያው ቤተ መዛግብት፣ ቤተልሔም(አፅንኦባእት)፣ የተጋድሎ ቦታ አፅመቅዱሳን የተለያዩ መገልገያዎች እና ቅርሶች ይገኛሉ፡፡