Friday, March 30, 2012

የለገዳዲ የቅድስት ኪዳነ ምህረት ፅላት ተአምር

     /በደረጀ ነጋሽ ዘወይንዬ/
        ዓርብ የካቲት 16/2004 ዓ.ም በጠዋቱኑ እጅግ በርካታ ምዕመናን በቅርብ በተገኘው የለገዳዲ ኬማ ዋሻ ፍልፍል ቤተክርስቲያን በአግራሞትና አድናቆት ተሰብስበዋል፡፡ በአካባቢው ድንኳኖች ተጥለዋል፡፡ አንዳንዶች ዋሻ ሲጎበኙ ሌሎች ደግሞ ፀበል ይጠመቃሉ፡፡ አንዳንዶች ይፀልያሉ ሌሎች ደግሞ ይነጋገራሉ፡፡ የከተማው ወይዛዝርት ለመስተንግዶው ይፋጠናሉ፡፡ እሺ ብላ ከዋሻው ትወጣ ይሆን? ወደ ዋሻው ካልተመለሰችስ? ብቻ የየራሳቸውን አስተያየት ይሰጣሉ፡፡ ለገዳዲ ከተማ ከአዲስ አበባ 25ኪ.ሜ ርቀት ላይ በኮተቤ መስመር ለገጣፎን አልፈው የምትገኝ ከተማ ስትሆን በወታደር ማሰልጠን፣ በትምህርት ስርጭት እና በውሃ አቅርቦት ትታወቃለች፡፡ ለገዳዲ ማለት በኦሮምኛ የጠጅ ወንዝ ማለት ነው፡፡ በዚህ ቦታ ገበሬዎች የፈረሰ ቤተክርስቲያን፤ ፀበል ይገኛል፣የአባቶቻችን መካነ መቃብር እዚህ ነው እያሉ በጉልበት ያለፍቃዳቸው አስፈራርተዋቸው ቦታውን ለኤንጂኦ ተሰጠ፤ አራት ዓመት ምንም ሳይሰራበት ቆየ፡፡ በብዙ ተንኮል ያገኘውን የቤተክርስቲያን የሃይማኖት ቦታ ሊሠራበት አጥር ማጠር ሲጀመር ዋሻ እንዳለ ለአባቶቻችን በህልም ታያቸው፡፡ ወደ ቦታው ሲሄዱ ከስር ከወንዝ አደገኛ ገደል ላይ ትንሽ ቀዳዳ ዐዩ፡፡ አፈር ሲቆፍሩ ፍልፍል ዋሻውን አገኙ፤ ዋሻው በሶስት ይከፈላል፡፡ የመጀመሪያው ቤተ መዛግብት፣ ቤተልሔም(አፅንኦባእት)፣ የተጋድሎ ቦታ አፅመቅዱሳን የተለያዩ መገልገያዎች እና ቅርሶች ይገኛሉ፡፡
   

Monday, March 26, 2012

የለገዳዲ ቅድስት ኪዳነ ምህረት ፅላት ከድንኳን ወደ መቃኞ ገባች


     (ማህበረ ቅዱስ አሞኒ መጋቢት 17/2004) ለገዳዲ ዋሻ ኪዳነ ምህረት በኮተቤ መስመር ከአዲስ አበባ 25 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ከለገጣፎ ከተማ አለፍ ብላ የምትገኝ ስትሆን እናት አባቶቻችን በሐይማኖት ጠብቀው ጽላተ ሙሴን ከአጽራረ ቤተ ክርስቲያን ለመጠበቅ ፍልፍል አብያተ ክርስቲያን ፈልፍለው ለእኛ ለልጆቻቸው ካቆዩልን የበረከት ስፍራ አንዱ ነው፡፡ በዚህ የበረከት ስፍራ የፈረሰና ቅርፁ ያልጠፋ ቤተ መቅደስ፣

Wednesday, March 21, 2012

በአሰቦት ገዳም የአብነት ተማሪ የሆነው የ7 ዓመቱ ሕፃን ናታን አንበስ ባልታወቁ ታጣቂዎች በ3 ጥይት ተመትቶ ተገደለ


በምዕራብ ሐረርጌ ሜኤሶ ወረዳ በአሰቦት ሥላሴና አባ ሳሙኤል ዘደብረ ወገግ ገዳም የአብነት ተማሪ የሆነው የ7 ዓመቱ ሕፃን ናታን አንበስ ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ላይ ማንነታቸው ባልታወቁ ታጣቂዎች በ3 ጥይት ተመትቶ መገደሉን የገዳሙ ዋና መጋቢና ምክትል አበምኔት አባ ዘወልደ ማርያም ገለጹ፡፡ ከአባ ሳሙኤል ገዳም በተወሰኑ ሜትሮች ርቀት ላይ ከእናቱ ጋር ወደ ገዳሙ በመውጣት ላይ እያለ ከእናቱ እጅ ቀምተው በመውሰድ ፊት ለፊቷ በሦስት ጥይት ገድለውት ሊያመልጡ ችለዋል፡፡ በእናትየው ጩኸትና በጥይት ድምጽ የተደናገጡት መነኮሳት ገዳዮቹን ለመያዝ ያደረጉት ጥረት ሳይሳካ ቀርቷል፡፡

የገዳሙ መነኮሳት እንደገለጹት

የዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስን ገዳም ለዘለቄታው በእሳት በማይጠቃበት መልኩ ለማቋቋም



ገዳሙ በመከላከሉ ሥራ ከፍተኛ የኢኮኖሚ እና የአካባቢ ጉዳት ደርሶበታል፡፡ እነሆ ገዳሙን መርዳት የምትፈልጉ ምእመናን የገዳሙ የባንክ አድራሻ የሚከተለው ነው፡፡
ለዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ
ደብረ ዘይት ቅርንጫፍ
የባንክ ቁጥር 19789
ደብረ ዘይት
(በአካውንቱ የላካችሁ ምእመናን በኢሜይል አድራሻ dkibret@gmail.com መላካችሁን ብትገልጡልን ለገዳሙ መልእክቱን ለማቀበል ይረዳናል)
እስካሁን በሁለት ቦታዎች ከሚታየው ጢስ በቀር የተነሣ እሳት የለም፡፡ እግዚአብሔር ጸሎታችንን ሰምቷል፤ ድካማችንንም ተቀብሏል፡፡

በአራት ቀን ውስጥ ከተቃጠለው የዝቋላ ገዳም ደን በከፊል

 

የዝቋላን ገዳም እንታደግ!!!

በዝቋላ ገዳም እና አካባቢው ደን ላይ የተነሣውን እሳት ለማጥፋት ለሚደረገው ጥረት ለማድረግ የግል ልገሳዎን ይስጡ በሚል ሐሳብ በማ/ቅዱሳን የአሜሪካ ማዕከል፣ በሰንበት ት/ቤቶች አንድነት ጉባኤ እና በማኅበረ በዓለ ወልድ አስተባባሪነት በሰሜን አሜሪካ የምንገኝ ኦርቶዶክሳውያን አስቸኳይ የገንዘብ ማሰባሰብ ሒደት ላይ እንገኛለን። ዓላማው በአሁኑ ወቅት እሳቱን ለማጥፋት ከየአካባቢው በነቂስ ለወጣው ኢትዮጵያዊ ወገናችን ጉሮሮውን ማርጠቢያ ውኃ፣ ጉልበቱን መደገፊያ ዳቦ ማቅረቢያ እንዲሆን የታሰበ ነው። በባዶ እጁ፣ በቅጠል እና በአፈር ቋያ እሳት ለማጥፋት እየታገለ ላለው ወገን አለኝታነታችንን ለመግለጽ ነው። ስለዚህም በሚከተለው አድራሻ እየገባችሁ የግላችሁን ልገሳ መስጠት የምትችሉ መሆኑን በትህትና እናስታውቃለን። http://zekuala.mahiberekidusan.org/  

Tuesday, March 20, 2012

በአሁኑ ሰዓት በዝቋላ ገዳም ነገሮች እየተረጋጉ ነው ተባለ

 
     አልፎ አልፎ ገደሉ ሥር ከሚታየው ጭስ በስተቀር ይህ ነው የተባለ የጎላ እሳት አሁን የለም፡፡ ገዳሙ ምንም እንኳን  በአካባቢው ያለው ሙቀት ቀትር ላይ ሲጨምር የሚሆነው ባይታወቅም በአሁኑ ደረጃ ግን እሳቱ ከገደሉ በላይ እንዳይወጣ አካባቢውን የማጽዳት  እና    የእሳት መከላከያ የመሥራቱ ሥራ ተጠናክሯል፡፡

እሳቱ ሊቆም አልቻለም


Crater lake 2 

     በዝቋላ ደብረ ከዋክብት አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም የደን ቃጠሎ እየተባባሰ ነው፡፡ ዛሬ በደረሰን መረጃ በትላንትናው እለት ከአዲስ አበባ፣ ከደብረ ዘይት፣ ከናዝሪት እና ከተለያዩ ቦታዎች የሄዱ ምዕመናን እሳቱን ለማጥፋት ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ ቢገኙም በጣም አስቸጋሪ እንደሆነባቸው ለማወቅ ተችሏል፡፡ የደን ቃጠሎው ከገዳሙ በግምት ከ300 - 400 ሜትር ርቀት ዐርብ ዕሮብ በሚባለው የተራራው ገጽ በኩል፣ ጠበሉ የሚገኝበትን ጥቅጥቅ ያለ ጫካ እየከበበ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡ መነኮሳቱ ለኦሮሚያ ፖሊስ፣ ለፌደራል ፖሊስና ለአየር ኀይል እንዲሁም ለምእመናን የድረሱልን ጥሪ በማሰማት ላይ የሚገኙ ሲሆን ከተለያዩ አካባቢዎች የሚመጡት በጎ ፈቃደኞች መጥረቢያ፣ አካፋ እና መቆፈርያ እየያዙ ቢመጡ የመከላከሉን ሥራ የተቃና የሚያደርግ ሲሆን በተለይም አቅና የሚባለው የመቆፈርያ ዓይነት ለዚህ ሥራ አመቺ በመሆኑ ይህንን መሣርያ ይዘው እንዲመጡ ጥሪ አድርገዋል፡፡ በቃጠሎ ጉዳት የደረሰባቸው ምእመናን እንደሚገኙ ከቦታው የደረሰን መረጃ የሚያመለክት ሲሆን በከፍተኛ ጥምና ረሃብ ላይ ለሚገኙ ምእመናን ውኃና ምግብ እንደሚያስፈልጋቸው ጭምር ገልጸዋል፡፡

እግዚአብሔር አምላክ ምህረቱን ያውርድልን አሜን!!!

Monday, March 19, 2012

ክተት ወደ ዝቋላ

Mount Zuqualla from the North 

ከአዲስ አበባ በቅርብ ርቀት የሚገኘው የዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳምደን በመንደድ ላይ መሆኑን የገዳሙ አባቶች እየተናገሩ ነው፡፡ እሳቱ መንደድ ከጀመረ ወደ ሃያ አራት ሰዓት ሊጠጋ ነውም ተብሏል፡፡ መንግሥት ከአካባቢው የውኃ ቦቴዎችን እና ወታደሮችን በማንቀሳቀስ ውኃውን ለማጥፋት ጥረት እያደረገ ቢሆንም እሳቱ ግን ወደ ገዳሙ በመጠጋት ላይ ነው፡፡
አሁን አማራጫችን አንድ ብቻ ነው፡፡ የዝቋላን ገዳም ከማጣታችን በፊት ያለንን ነገር ሁሉ ይዘን በተገኘው ትራንስፖርት ወደ ዝቋላ መትመም ብቻ፡፡ ወንበር ማርያም ድረስ የውኃ ቦቴዎቹ ሊደርሱ ይችላሉ፡፡ ከዚያ በኋላ ያለውን ባገኘነውዕቃ ሁሉ ውኃውን ይዘን በመውጣት መረባረብ፡፡ ያለበለዚያ ግን የዝቋላ አቡነገብረ መንፈስ ቅዱስ ገዳም ከጥቂት ሰዓታት በኋላ ወደ ታሪክነት ይቀየራል፡፡
እነሆ ክርስትናችን የሚፈተንበት፣ ኢትዮጵያዊነታችንም የሚለካበት ጊዜ መጣ፣በእሳት ተቃጥለው ያቆዩትን ገዳም ከእሳት ማዳን ካልቻልን እንግዲህ የኛ መኖር ትርጉሙ ምንድን ነው?
መኪኖች ያሏችሁ አንቀሳቅሱ፣ ጉልበት ያላችሁ ተንቀሳቀሱ፣ ሌላም አማራጭያላችሁ በፍጥነት ተጓዙ፣እሳቱን በእምነት እንቅደመው፡፡

Sunday, March 18, 2012

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሲኖዳ 3ኛ አረፉ


 ግብፅ ቤተ ክርስቲያን ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳትና የቅዱስ ማርቆስ መንበር 117ኛ ፓትሪያርክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሲኖዳ 3ኛ መጋቢት 8 ቀን 2004 ዓ.ም በ 88 ዓመታቸው በካንሰር ሕመም ምክንያት ከዚህ ዓለም ድካም ዐርፈዋል፡፡
በሰሜናዊ ግብፅ፣ አስዩት ውስጥ ሐምሌ 27 ቀን 1915 . ሲወለዱ ናዚር ጋይድ የሚል መጠሪያ ከቤተሰባቸው የተሰጣቸው ቅዱስነታቸው፣  ቅስናን ሲቀበሉ አባ እንጦንስ ተብለው ይጠሩ የነበር ሲሆን አቡነ ሲኖዳ የተባሉት 1955 . የክርስትና ትምህርት ኤጲስ ቆጶስ ተብለው በተሾሙበት ወቅት ነበር፡፡ ቅዱስነታቸው አቡነ ሲኖዳ የቅብጥ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን 117 ፓትርያርክ ሆነው በወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ መንበር ላይ የተሾሙት ከተአምር ሠሪው ፓትርያርክ ከብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ቄርሎስ 6 በኋላ ኅዳር 4 ቀን 1964 . ነበር፡፡