የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ሰኞ ዕለት ባደረገው ስብስባ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ዓቃቤ መንበር ሆነው መመረጣቸውን የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ጸሐፊ ብፁዕ አቡነ ሕዝቅኤል አስታወቁ፡፡
ብፁዕ አቡነ ናትኤል የአርሲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ
ብፁዕነታቸው ሰኞ ዕለት ከቀኑ 9፡30 ሰዓት ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት ምልዓተ ጉባኤው ሰኞ ባደረገው ስብሰባ ለቅዱስ ፓትርያርኩ ሥርዓተ ቀብር የሚመጡ የሀገር ውስጥም ሆነ የውጭ ሀገር እንግዶች በአግባቡ ማስተናገድ እንዲቻልና መንበርም ያለ ኃላፊ አንድም ቀን ማደር ስለማይገባ በሕገ ቤተ ክርስቲያን አንቀጽ 17 መሠረት በማድረግ ቀደምትነት ካላቸው ብፁዓን አባቶች መካከል ብፁዕ አቡነ ናትናኤል መመረጣቸውን ይፋ አድርገዋል፡፡
ከዚህ በተያያዘ መልኩም ከዓቃቤ መንበር ብፁዕ አቡነ ናትናኤልና ከቋሚ ሲኖዶስ ጋር በመሆን ሥራውን የሚያከናውኑ ሥራ አስፈጻሚዎች ምልአተ ጉባኤው መሰየሙን ስማቸውን ጠቅሶ አስረድተዋል፡፡ በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ የተሰየሙ ብፁዓን አባቶች ስም ዝርዝር እንደሚከተለው ነው፡፡