Monday, May 7, 2012

አንቲ ምሥራቅ ወወልድኪ ፀሐየ ጽድቅ፤


አንቺ ምሥራቅ ነሽ ልጅሽም እውነተኛ ፀሐይ ነው። /ድጓ/

ሊቀ ጠበብት ሐረገወይን አገዘ
     የቤተ ክርስቲያን አባት የእግዚአብሔር ወዳጅ ሆኖ ስለእመቤታችን ያልዘመረ ፣ያላመሰገነ ያልጻፈ የለም።ታላቁ የቤተ ክርስቲያናችን ሊቅ ቅዱስ ያሬድ የሚገባውን ንጽጽራዊ ምሳሌ ለሚገባት ወላዲት አምላክ ሰጥቶ አመስጥሮ ዘመረ። እንዲህ በማለት “ አንቺ የብርሃን መውጫ ምሥራቅ ነሽ፤ልጅሽም ከብርሃን የተገኘ ብርሃን እውነተኛ ፀሐይም ነው።”