አንቺ ምሥራቅ ነሽ ልጅሽም እውነተኛ ፀሐይ ነው። /ድጓ/
ሊቀ ጠበብት ሐረገወይን አገዘ
የቤተ ክርስቲያን አባት የእግዚአብሔር ወዳጅ ሆኖ ስለእመቤታችን ያልዘመረ ፣ያላመሰገነ ያልጻፈ የለም።ታላቁ የቤተ ክርስቲያናችን ሊቅ ቅዱስ ያሬድ የሚገባውን ንጽጽራዊ ምሳሌ ለሚገባት ወላዲት አምላክ ሰጥቶ አመስጥሮ ዘመረ። እንዲህ በማለት “ አንቺ የብርሃን መውጫ ምሥራቅ ነሽ፤ልጅሽም ከብርሃን የተገኘ ብርሃን እውነተኛ ፀሐይም ነው።”